ካርድ በሐሳብን የመግለጽ ነጻነት፣ የጥላቻ ንግግር እና ምርጫ ጉዳይ የውይይት መድረክ አሰናዳ

CARD_and_AMLO

ካርድ ከአምሃ መኮንን እና አጋሮቹ የሕግ ቢሮ እና የኢትዮጵያ ዲጂታል መብቶች ቡድን ጋር በመተባበር የውይይት መድረክ አሰናዳ። የውይይት መድረኩ “ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት፣ የጥላቻ ንግግር እና ምርጫ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እና ብዙኀን መገናኛዎች በተገኙበት የካቲት 21 ፣ 2012 በኢንተር ኮንቲነንታል አዲስ ሆቴል ለግማሽ ቀናት ተካሒዷል። የውይይት መድረኩ ያስፈለገው ዜጎች ሐሳባቸውን በነጻነት በሚገልጹበት ጊዜ የጥላቻ ንግግርን እና የሐሰት መረጃን ከማሰራጨት እንዲቆጠቡ እንዲሁም መንግሥት የጥላቻ ንግግሮችን በሕግ አግባብ ለመቆጣጠር ሲሞክር ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ለማድረግ የሚያስችሉ ሐሳቦች ላይ ለመምከር ነው። 

በውይይት መድረኩ ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብኣዊ መብቶች ማዕከል ዳይሬክተር ወንድማገኝ ታደሰ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡ ሲሆን፣ አምሃ መኮንንም በቅርቡ በፀደቀው የፀረ ጥላቻ ንግግር አዋጅ ይዘት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የውይይት መድረኩ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች አምሃ መኮንን እና ወንድማገኝ ታደሰ መልስ እንዲሰጡ አስችሏል። 

ጥናቱ እና የውይይት መድረኩን ድጋፍ እንዲካሔድ ድጋፍ ያደረገው ናሽናል ኢንዶውመንት ፎር ዲሞክራሲ ነው።

Add a review

The comment language code.

Restricted HTML

  • Allowed HTML tags: <a href hreflang> <em> <strong> <cite> <blockquote cite> <code> <ul type> <ol start type> <li> <dl> <dt> <dd> <h2 id> <h3 id> <h4 id> <h5 id> <h6 id>
  • Lines and paragraphs break automatically.
  • Web page addresses and email addresses turn into links automatically.