ዴሞክራሲን ብቸኛው የጫወታ ሕግ ማድረግ!
ሴንተር ፎር አድቫንስመንት ኦፍ ራይትስ ኤንድ ዴሞክራሲ (የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል /ካርድ/)፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ፣ በአዋጅ ቁጥር 1113/2011፣ በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን መዝገብ ቁጥር 4307 ሐምሌ 17፣ 2011 የተመዘገበ፣ ቦርድ መር፣ የአገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ነው። ካርድ በሰብዓዊ መብቶች እሴት ላይ የቆመ ዴሞክራሲያዊ ባሕል ያበበባት ኢትዮጵያን የማየት ራዕይ ሰንቆ፥ የኢትዮጵያ ዜጎች እና የዜጎች ማኅበራት ለሰብዓዊ መብቶች መከበር በመሟገት ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እንዲያሰፍኑ የሚያስችላቸውን የአቅም ግንባታ ማድረግ ተልዕኮ በማንገብ እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ነው። ተጨማሪ ያንብቡ...
የካርድ ማንነት
ካርድ በሰብዓዊ መብቶች እሴቶች የታነፀ ግንዛቤ ማሳደግ፣ ማደራጀት፣ እና የፖለሲሲ ሙግት በማድረግ ዴሞክራሲያዊ የብዙኃን ባሕል እና ሕዝባዊ ንቅናቄን ለመፍጠር እየተጋ ያለ ድርጅት ነው።
የካርድ ራዕይ
በሰብዓዊ መብቶች እሴት ላይ የቆመ ዴሞክራሲያዊ ባሕል ያበበባት ኢትዮጵያን ማየት።
የካርድ ተልዕኮ
የኢትዮጵያ ዜጎች እና የዜጎች ማኅበራት ለሰብዓዊ መብቶች መከበር በመሟገት ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እንዲያሰፍኑ የሚያስችላቸውን የአቅም ግንባታ ማድረግ።
የካርድ አንኳር ዓላማዎች
ካርድ፣ በሕግ የተመዘገበባቸው የሥራ ኃላፊነቶቹ የሚከተሉት ናቸው፦
- በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ባሕል እንዲያብብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን መሥራት
- የሰብዓዊ መብቶች እና የዴሞክራሲ ዕድገት ደረጃን በመከታተል እና በመገምገም መንግሥታዊ የሆኑ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት ተጠያቂነት እንዲያዳብሩ ማድረግ
- የዴሞክራሲ ግንባታን ለማገዝ የሚያስችሉ ተፅዕኖዎችን ለማድረግ የምርምር ሥራዎችን መሥራት፣ የምክክር መድረኮችን ማዘጋጀት፣ እና የማግባባት ሥራዎችን መሥራት
- ለዴሞክራሲ ተቋማት ቴክኒካዊ እና ሙያዊ ድጋፍ መስጠት
- ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበራቸውን ለማረጋገጥ የፖሊስ ማቆያዎችን፣ የማረሚያ ቤቶችን አያያዝ እና የፍርድ ቤቶችን ሒደት መከታተል እና መገምገም
ምርጫዎችን መታዘብ፣ የዜግነት እና የመራጮች ትምህርት መስጠት
Programs
-
የዜግነት ተሳትፎ
ይህ ፕሮግራም የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች እና ወጣት መሪዎች ሙያዊ እና ቁሳዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ በማገዝ፣ የግል ሙከራቸውን ተቋማዊ፣ እንዲሁም ኢ-መደበኛ ንቅናቄያቸውን መደበኛ እንዲያደርጉ እና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር እና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ማኅበራዊ መሠረት ለማቆም የሚሠራ መርሐ ግብር ነው።
-
የሚዲያ አረዳድ ክኅሎት
ይህ ፕሮግራም የሚዲያ ባለሙያዎችን እና የበይነመረብ አምደኞችን ሙያዊ ብቃት እና ሥነ ምግባር የሚያሳድጉ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን በማቅረብ፣ የሐሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል፣ በጋዜጠኞች ማኅበራት መካከል ትብብር በመፍጠር ነጻ እና ጠንካራ የሚዲያ ማኅበረሰብ እና ምኅዳር እንዲፈጠር የሚሠራ መርሐ ግብር ነው።
-
የወጣቶች እና ሴቶች አቅም ግንባታ
ይሀ ፕሮግራም የወጣቶች እና ሴቶችን አቅም በማሳደግ ፍትሐዊ እና ሁሉን አካታች እንዲሁም አሳታፊ ስርዓተ ማኅበር እንዲፈጠር በዕውቀት እና ሥልጠና የታገዘ ዴሞክራሲያዊ እና የሰብዓዊ መብቶች ንቅናቄ የብዙኃን መሠረት እንዲኖረው የሚሠራ መርሐ ግብር ነው።
-
የዲጂታል መብቶች
ይህ ፕሮግራም የበይነመረብ ተጠቃሚ ዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እና ደኅንነታቸው እንዲጠበቅ የአድቮኬሲ/ሙግት እና የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥልጠናዎችን በመስጠት የዜጎችን ዲጂታል ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የሚሠራ መርሐ ግብር ነው።
-
የዴሞክራሲያዊነት ምዘና
ይህ ፕሮግራም በሙከራ ላይ ያለ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ውስጥ ያሉ ክልሎችን እና የፌዴራል ከተሞችን ዓመታዊ የዴሞክራሲያዊነት ሒደት በመገምገም በየዓመቱ ውጤቱን ይፋ በማድረግ ሒደቱን መከታተል እና ሕጋዊ እና ተግባራዊ የማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ የሚሠራ መርሐ ግብር ነው።