ዴሞክራሲን ብቸኛው የጫወታ ሕግ ማድረግ! 

 

ሴንተር ፎር አድቫንስመንት ኦፍ ራይትስ ኤንድ ዴሞክራሲ (የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል /ካርድ/)፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ፣ በአዋጅ ቁጥር 1113/2011፣ በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን መዝገብ ቁጥር 4307 ሐምሌ 17፣ 2011 የተመዘገበ፣ ቦርድ መር፣ የአገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ነው። ካርድ ሰብዓዊ መብቶች የተከበሩባት እና ዴሞክራሲያዊ ባሕል ያበበባት ኢትዮጵያን የማየት ራዕይ ሰንቆ፥ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር እና ለዴሞክራሲያዊ ባሕል ግንባታ የተመቻቸ የሲቪክ፣ የሚዲያ፣ እና የዲጂታል ምኅዳር እንዲገነባ እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ነው። ተጨማሪ ያንብቡ...

 


የካርድ ማንነት

ካርድ በሰብዓዊ መብቶች እሴቶች የታነፀ ግንዛቤ ማሳደግ፣ ማደራጀት፣ እና የፖለሲሲ ሙግት በማድረግ ዴሞክራሲያዊ የብዙኃን ባሕል እና ሕዝባዊ ንቅናቄን ለመፍጠር እየተጋ ያለ ድርጅት ነው። 

የካርድ ራዕይ
ሰብዓዊ መብቶች የተከበሩባት እነ ዴሞክራሲያዊ ባሕል ያበበባት ኢትዮጵያን ማየት።  

የካርድ ተልዕኮ
ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና ዴሞክራሲያዊ ባሕል ግንባታ የተመቻቸ የሲቪክ፣ የሚዲያና፣ የዲጂታል ምኅዳር እንዲጎለበት መሥራት ነው። 


የካርድ አንኳር ዓላማዎች
ካርድ፣ በሕግ የተመዘገበባቸው የሥራ ኃላፊነቶቹ የሚከተሉት ናቸው፦

  • የዲሞክራሲ ዕሴቶችን በማስረፅ፣ ግንዛቤን በማሳደግና የዲሞክራሲ ልምምድ መድረኮችን በማዘጋጀት ዴሞክራሲያዊ ባሕል በኢትዮጵያ እንዲጎለብት መሥራት፣

  • በመንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የሚያግዙ ወቅታዊ የመከታተል፣ የመሰነድ፣ ይፋ ማድረግ እና የሙግት ሥራዎችን መሥራት፣

  • አስፈላጊ የሆኑ ለውጦችን ለማምጣት የፖሊሲ ጥናትና ምርምር እንዲሁም ምክክር እና ግፊት ማድረግ፣

  • ለዴሞክራሲ ተቋማት ሙያዊ እና ቴክኒካዊ ድጋፍ ማድረግ፣

  • የሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ የኢትዮጵያን ሕግ መሠረት በማድረግ የፖሊስ ማቆያዎችን፣ ማረሚያ ቤቶችን እና የፍርድ ቤት ሒደቶችን መከታተል፣ መሰነድ እና ሪፖርት ማውጣት፣

  • የሚዲያ ምኅዳሩ እንዲሰፋ እና የጋዜጠኞች ሙያተኝነት ሥነ ምግባር እንዲጎለብት መሟገት እና የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረግ፣

  • የዲጂታል መብቶች እንዲከበሩ እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚዎች ደኅንነት እንዲጠበቅ መሟገት እና ድጋፍ መስጠት፣ 

  • ምርጫዎችን መታዘብ፣ የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት መስጠት።

Programs